በቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የግድያ ሙከራ የተጠረጠረ ግለሰብና አንድ ታዳሚ ተገደሉ

የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትና የሪፐብሊካን ፓርቲ 2024 ፕሬዚደንታዊ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ የተደረገባቸው ቅዳሜ ዕለት በፔንሲልቫኒያ የምረጡኝ ዘመቻ ንግግር እያደረጉ ሳለ ነው።

Election 2024 Trump

Republican presidential candidate former President Donald Trump is helped off the stage at a campaign event in Butler, Pa., on Saturday, July 13, 2024. Source: AP / Gene J. Puskar/AP

የአካባቢው ባለስልጣናት እንዳስታወቁት በቀድሞው ፕሬዚደንት ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በዶናልድ ትራምፕ ልዩ የደህንነት ጥበቃ አባላት መገደሉንና የአንድ ታዳሚ ግለሰብ ሕይወት መቀጠፉንም ገልጠዋል።

ባለስልጣናቱ አክለውም ሁለት የምረጡኝ ዘመቻ ታዳሚዎች መቁሰላቸውንም አክለው ተናግረዋል።

በወቅቱ በርካታ የተኩስ ድምፆች ተሰምተዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ባይደን ክስተቱን አውግዘው ለቀድሞው ፕሬዚደንት ደህንነት እንደሚፀልዩ ገለጠዋል።
የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚም ክስተቱን አውግዘዋል።

Share
Published 14 July 2024 11:45am
Updated 14 July 2024 11:49am
By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends