የአካባቢው ባለስልጣናት እንዳስታወቁት በቀድሞው ፕሬዚደንት ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በዶናልድ ትራምፕ ልዩ የደህንነት ጥበቃ አባላት መገደሉንና የአንድ ታዳሚ ግለሰብ ሕይወት መቀጠፉንም ገልጠዋል።
ባለስልጣናቱ አክለውም ሁለት የምረጡኝ ዘመቻ ታዳሚዎች መቁሰላቸውንም አክለው ተናግረዋል።
በወቅቱ በርካታ የተኩስ ድምፆች ተሰምተዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ባይደን ክስተቱን አውግዘው ለቀድሞው ፕሬዚደንት ደህንነት እንደሚፀልዩ ገለጠዋል።
የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚም ክስተቱን አውግዘዋል።