የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተቋሙን አፈጻጸም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ ተቋሙ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል።
ገቢው ካለፈ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ21 በመቶ ወይም 16 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳይቷል። ገቢው ከእቅድ በላይ 103 ነጥብ 6 በመቶ ሆኗል። በዚህም 21 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘትም ችሏል ብለዋል።
ከገቢው 39 ነጥብ 4 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት የተገኘ መሆኑን ገልጸው፤ 27 ነጥብ 7 በመቶው ከዳታና ኢንተርኔት የተገኘ ነው። ገቢው ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞች ቁጥርን ካለፈው ዓመት በ8 ነጥብ 9 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል።
የቴሌብር ደንበኞት ቁጥርም 47 ነጥብ 55 ሚሊዮን መድረሱን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ አንድ ነጥብ 81 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር ተከናውኗል።
አገልገሎቱ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ 2ነጥብ55 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ማንቀሳቀስ መቻሉንም ጠቁመዋል።