የአማራ ክልል ዳኞች ማኅበር የሕፃን ሔቨን ይግባኝ በፍርድ ቤት መታየት ዳኞች ሕግን መሠረት አድርገው "በነፃነት እንዳይሠሩ ያልተገባ ጫና" ያሳድራል ሲል ተቃውሞ አሰማ

በሕፃን ሔቨን ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽሞ ለሕልፈት በመዳረግ የ25 ዓመት ጽኑ እሥራት የተፈረደበት ጌትነት ባይህ ያቀረበውን ይግባኝ ፍርድ ቤቱ በማየቱ የተጀመረውን የተቃውሞ ዘመቻ የአማራ ክልል ዳኞች ማኅበር አውግዟል።

Heaven A.png

Heaven Credit: PD

ማኅበሩ፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚንስቴርና ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚያካሂዱት ዘመቻ ከዳኝነት ነፃነትና ከሕግ የበላይነት መርህ ያፈነገጠና ዳኞች ሕግን መሠረት አድርገው "በነፃነት እንዳይሠሩ ያልተገባ ጫና" እንደሚፈጥር ገልጧል።

በአገሪቱ ሕግ በወንጀልም ኾነ በፍትሐብሄር የተፈረደበት ወገን ይግባኝ የመጠየቅ ሕገመንግሥታዊ መብት እንዳለው የጠቀሰው ማኅበሩ፣ ግለሰቡ ይግባኝ ማቅረብ የለበትም የሚል ዘመቻ ማድረግ "በሕግ የመዳኘት መብትን አደጋ ላይ የሚጥል" እና በፍርድ ቤቱ ላይ "ያልተገባ ጫና በማሳደር የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት" ይጥሳል ብሏል።

ሚንስቴሩ ይግባኝ መቅረቡን ተቃውሞ በጉዳዩ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚሠራ መግለጡ ይታወሳል።


Share
Published 19 August 2024 3:16pm
Updated 19 August 2024 3:23pm
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends